አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 4 /2018 ዓ.ም (የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት)
በዛሬው ዕለት በፀደይ ባንክ ዋናው መ/ቤት በአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት እና በፀደይ ባንክ መካከል በጋራ ለመስራት የሚያስችል የመግባቢያ ስምምነት የተፈረመ ሲሆን፣ ይህም በአማራ ክልል በየደረጃው ያሉ ፍ/ቤቶች ዳኞችና የአስተዳደር ሠራተኞችን በሥራ ላይ ማቆየት የሚቻልባቸው ጉዳዮችን የሚመለከት ነው።
ስምምነቱን የፈረሙት የአማራ ክልል ጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዘዳንት አለምአንተ አግደው፣ ፀደይ ባንክ የፍ/ቤት መጠናከር ለአገር ያለውን ፋይዳ በመረዳት በጋር ለመስራት የወሰደውን እርምጃ ያደነቁ ሲሆን፣ የፀደይ ባንክ ፕሬዘዳንት ዮሃንስ አያሌው (ዶ/ር) በበኩላቸው፣ ባንኩ ዘመናዊና በቴክኖሎጅ የተደገፉ አዳዲስ የአሰራር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ላይ ያለ እና ለሕዝብ ተጠቃሚነት እየሰራ መሆኑን ጠቅሰው፣ ሁሉአቀፍ የለውጥ ሥራ ውስጥ ከሚገኘው የክልሉ ጠቅላይ ፍ/ቤት ጋር በጋራ ለመሥራት በመስማማታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።








